Page 1 of 1

አባ ገዳ ጎበና የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አባል የሆነው ልጃቸው መገደሉን ከማኅበራዊ ሚዲያ መስማታቸውን ተናገሩ

Posted: 22 Apr 2024, 12:40
by Za-Ilmaknun
የቱለማ አባ ገዳ የሆኑት አባ ገዳ ጎበና ሆላ ኢሬሶ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አባል የሆነው ልጃቸው መገደሉን ከማኅበራዊ ሚዲያ መስማታቸውን ለቢቢሲ ተናገሩ።

ከአንድ ሳምንት በፊት በኦሮሚያ ክልል የምዕራብ አርሲ ዞን ኮሚዩኒኬሽን መንግሥት ‘ሸኔ’ የሚለው ቡድን አባል ነው ያለው የአባ ገዳ ጎበና ልጅ “ሰላማዊ ሰዎችን ለመግደል ሲንቀሳቀስ እርምጃ ተወስዶበታል” ብሎ ነበር።

የቱለማ አባገዳ እና የኦሮሞ አባገዳዎች ኅብረት ፀሐፊ የሆኑት አባ ገዳ ጎበና ሆላ፣ ፎሌ ጎበና የሚባለው ልጃቸውን መገደል የሰሙት በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ከሚሠራጨው ወሬ መሆኑን እና አስካሁን ምንም ማረጋገጫ እንዳላገኙ ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ተናግረዋል።

ከጥቂት ወራት በፊት አባ ገዳ ጎበና ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ቤታቸው ላይ ብርበራ በተደረገበት ወቅት ከወላጅ አባታቸው የወረሱት የጦር መሳሪያ መወሰዱን እና ክስተቱን ተከትሎ በቤተሰብ አባላት ላይ ከፍተኛ መደናገጥ መፈጠሩን ተናግረው ነበር።

አባ ገዳ ጎበና ከቀድሞ የቱለማ አባ ገዳ በየነ ሰንበቶ መስከረም 20/2011 ዓ.ም. በኦሮሞ ሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ የሆነውን ባሕላዊ ሥልጣንን መረከባቸው ይታወሳል።

https://www.bbc.com/amharic/articles/c72p687d4ywo