ደቡብ ሱዳን እና የአዲስ አበባው የሰላም ድርድር

በደቡብ ሱዳን የተሰማራው የተመድ ሰላም አስከባሪ ጓድ፣ በምህጻሩ አንሚስ ወጥረት ወደቀጠለበት የዩኒቲ ግዛት 150 ሰላም አስከባሪ ወታደሮች እንደሚልክ አስታውቋል። የወታደሮቹ ተልዕኮ በመንግሥቱ ጦር እና በዓማፅያን መካከል የሚካሄደው ውጊያ ዒላማ ያደረገው የአካባቢው ሲቭል ሕዝብ ጉዳት እንዳይደርስበት መከላከል እንደሆነ አንሚስ አመልክቷል።