ዘርፈ ብዙዋ የህክምና ሰው

የመጀመሪያዋ ሴት የህክምና ፕሮፌሰር ናቸው፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ታሪክ ደግሞ ይህንን ማዕረግ በማግኘት የቀደሟቸው አንድ ሴት ብቻ ናቸው፡፡ በመምህርነት፣ በተማራማሪነት እና በሀኪምነት ላለፉት 33 ዓመታት እያገለገሉ ይገኛሉ፡፡ የስኳር ህመምን የተመለከተ አንድ መጽሐፍም አሳትመዋል፡፡ ፕሮፌሰር የወይንሐረግ ፈለቀ ይባላሉ፡፡