አዲሱ የጀርመን ጥምር መንግሥትና የአፍሪቃ ፖሊሲዉ

በአዲሱ የጀርመን ጥምር መንግሥት በግሉ የንግድ ዘርፍ ተጨማሪ የልማት እርዳታ በማድረግ ለአፍሪቃ ቀደምቱን ቦታ መስጠት ይፈልጋል። የፖለቲካ ጉዳይ ተንታኞች በበኩላቸዉ፤ መንግሥት ለአፍሪቃ ያቀደዉ ልማታዊ የትብብር ዉል ባለፈዉም መንግሥት እቅድ ላይ የሰፈረ ነበር ሲሉ እቅዶቹ ባዶ ተስፋ ሆነዉ እንዳይበኑ ከወዲሁ ያስጠነቅቃሉ።