አፍሪቃን የሚያሰጋ አዲስ የውጭ እዳ ቀውስ

በአውሮጳ በወቅቱ የብድር ወለድ ዝቅተኛ መሆኑ አፍሪቃን ለግል ባለሀብቶች አማላይ አድርጓታል። ወለድ ዝቅ ማለቱ ግን በአፍሪቃ ብድር ከፍ የሚልበትን ቀውስ ስጋት ይዞ እንደሚመጣ ለጎርጎሪዮሳዊው 2018 ዓም የወጣ የውጭ እዳን የተመለከተ አንድ ዘገባ አስጠንቅቋል።