ስፖርት፤ መጋቢት 10 ቀን፣ 2010 ዓ.ም 

በአፍሪቃ የኮንፌዴሬሽን ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታ አዲስ መጪው ወላይታ ዲቻ አንጋፋው የግብጽ የእግር ኳስ ቡድን ዛማሌክን ከውድድር አሰናብቶ ጉድ አሰኝቷል። ሌላኛው የኢትዮጵያ አንጋፋ ቡድን ቅዱስ ጊዮርጊስ ግን በኡጋንዳው ካምፓላ ካፒታል ሲቲ አውቶሪቲ (KCCA) ከቻምፒየንስ ሊግ ተሰናብቷል።