የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃለ አቀባይ አቶ መለሰ አለም የማእከላዊ ማሰቃያ እስር ቤት ደብዳቢና ገራፊ እንደነበር ተጋለጠ ።

ተከሳሹ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃለ አቀባይ አቶ መለሰ አለም ድብደባ እንደፈፀሙበት ለፍርድ ቤት ገለፀ

~ “ጉራጌ በመሆኔ ብቻ ዘሬ እየተጠቀሰ ከፍተኛ ስቃይ ሲደርስብኝ ነበር”

~” ከደበደቡኝ ሰዎች መሀል የአሁኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ መለሰ አለም አንዱ ናቸው”

( በእነ ጌታሁን በየነ ክስ መዝገብ ተከሳሽ የሆነው ሰይፈ አለሙ መከላከያ ምስክር ከማሰማቱ በፊት ለፍርድ ቤት የሰጠውን ቃል ፍሬው ተክሌ እንደሚከተለው ፅፎታል)

“በማዕከላዊ ከመርማሪዎች ጋር ሳይሆን ጥቃትን ከሚያደርሱ አካላት ጋር ነበርኩ። እኔ የተያዝኩት አርባምንጭ ሆቴል ውስጥ ነው። የያዘኝም ደህንነት ነው። ይዞም ማዕከላዊ የሚባል ሲኦል ውስጥ ነው የከተተኝ የተረከበኝም ኮማንደር ተክላይ ነው። ይደበድቡኝ የነበሩት በጣም ብዙ ናቸው ሴቶችም አሉበት ከኮማንደር ተክላይ ጋር ሰክረው ነበር የሚደበድቡኝ

“ከሚደበድቡኝ ሰዎች መሀከል የአሁኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ መለሰ አለም አንዱ ነበር። በማዕከላዊ ጥቃት ይደርስብኝ የነበረው በቤሄሬ ነው ጉራጌ ሌብነት እንጂ ፖለቲካን የት ያውቃል እየተባልኩ ምራቅ እየተተፋብኝ ነበር ስደበደብ የነበረው

 

“ከዚህ በፊትም ማዕከላዊ ተይዘው የገቡ ብዙ ጉራጌዎች ተደብድበዎል ተኮላሽተዎል በዚህ ቤሄር ላይ እየደረሰ ያለው ጥቃት ሊቆም ይገባል። ሰውነቴ ላይ የሚታዩት እነዚህ ጠባሳዎች ከእናቴ ማህፀን ስወለድ ያገኘሆቸው ሳይሆኑ በማዕከላዊ በደረሰብኝ ድብደባ ምክንያት ሰውነቴ ላይ የቀሩ ናቸው። ይሄ ሁሉ ድብደባ ደርሶብኝ ሰውነቴም መግሎብኝ ህክምና እንኮን አለገኘሁም ነበር።

በጊዜው አብረውኝ የነበሩ እስረኞች ህክምና ያግኝ ብለው የረሀብ አድማ አድርገው ነበር ሀላፊዎቹም ህክምና ይደረግለተል ብለው ቃል ከገቡ በሆላ እኔን ጠርተው አንተን አናክምህም ብለው ማስታገሻ ብቻ ሰተውኛል። ስደበደብ የነበረውም የግንቦት ሰባት አመራር ነህ ተብዬ ነው።”

ሲል የተከሳሽነት ቃሉን የሰጠ ሲሆን ሶስት የመከላከያ ምስክሮች አቅርቦ አሰምቶል። ምስክሮቹም በወቅቱ መዕከላዊ አብረው መታሰራቸውን ገልፀዋል። ሰይፉ አለሙ ላይ ይደርስ የነበረውን ሰቃይ በድብደባ ምክንያት ሰውነቱ ላይ ይታዩ የነበሩ ቁስሎችን እና የህክምና እርዳታ እንዲያገኝ የረሀብ አድማ ማድረጋቸውን ገልፀው ለፍ/ቤቱ አስረድተዎል። ፍ/ቤቱም በመከላከያ ምስክሮች ላይ ብይን ለመስጠት ለሚያዚያ 16/2010 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል።