ከኢትዮጵያ ሞያሌ የተሰደዱት 10,557 ደረሱ

መጋቢት አንድ ቀን፣ 2010 ዓ/ም የመከላከያ ሠራዊት በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ሞያሌ ከተማ ጥቃት ካደረሰ በኋላ በከተማዋና በአከባቢዉ ከሚገኙ ቀበሌዎች የተፈናቀሉት ሰዎች ቁጥር ወደ 50ሺህ እንደሚሆን የከተማዉ ከንቲባ አቶ አስቻለዉ ዮሃንስ ለዶይቼ ቬሌ መናገራቸዉ ይታወሳል።