የኒውክለር ኃይል ማመንጫ ለኢትዮጵያ?

የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ከሁለት ሳምንት በፊት ወደ አፍሪቃ በመጡ ወቅት  ሀገራቸው የኒውክለር ኃይልን ለሰላማዊ አገልግሎት ለመጠቀም ከሚፈልጉ ሀገራት ጋር በትብብር እንደምትሰራ መናገራቸው ይታወሳል፡፡ በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታም ሀገሪቱ የኒውክለር ተቋም ለመገንባት ከሩሲያ ጋር ስምምነት ላይ መድረሷን አስታውቀዋል፡፡