ከእስር የተፈቱት የሳዑዲ ልዑል ተናገሩ

በሳዑዲ ዓረቢያ የጸረ ሙስና ኮሚሽን ተጠርጥረው ለ83 ቀኖች  በቁጥጥር ስር የሰነበቱት የሳዑዲ ታላቁ ባለሀብት አል ወሊድ ቢን ጥላል ለአጎታቸው ንጉስ ሰልማንም ሆነ ለአልጋወራሽ መሀመድ ቢን ሰልማን በየትኛውም መንገድ ድጋፋቸውን እንደሚሰጡ አስታወቁ።