የኬንያ ፕ/ምርጫ እና የኬምብሪጅ አናሊቲካ ተቋም ሚና 

ኬምብሪጅ አናሊቲካ የተባለው መረጃዎችን የሚገመግመው የብሪታንያውያን አማካሪ ተቋም በሚልዮን የሚቆጠሩ የፌስቡክ ተጠቃሚዎችን መረጃዎች ካለፈቃዳቸው በመውሰዱ በወቅቱ ትልቅ ወቀሳ ተፈራርቆበታል። እንደ ብሪታንያ ቴሌቪዥን ቻነል 4 ዘገባ፣ ተቋሙ የኬንያ ፕሬዚደንት ኡሁሩ ኬንያታ በ2017 ዓም ድጋሚ በተመረጡበትም ምርጫ ላይ እጁ አለበት ነው የተባለው።