ልዑል ሉዊ ዋጋሶሬ፤ የንጉሥ ልጅ የዲሞክራሲ ታጋይ

ሀገራቸው ነፃነቷን ከመቀዳጀቷ አንድ ዓመት ቀደም ብሎ ነበር የተገደሉት። ቡሩንዲ ሠላማዊ በኾነ ሽግግር ነጻነቷን እንድታውጅ የልዑል ሉዊ ዋጋሶሬ ተግባር ልዩ ሥፍራ ይሰጠዋል። ምንም እንኳ የንጉሥ ልጅ ቢኾኑም ስለ ዲሞክራሲ በመስበክ፤ የሀገሪቱ የመጀመሪያው ጠቅላይ ሚንሥትርም መኾን ችለዋል።