የተቃዋሚ ፓርቲዎች አስተያያት በአዲሱ ካቢኔ

ጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አህመድ በትናንትናዉ ዕለት ያዋቀሩት አዲስ ካቢኔ  የለዉጥ ሽታ የሌለዉና የህዝቡን ጥያቄ የሚመልስ አይደለም ሲሉ  አንዳንድ የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካዮች አስታወቁ።ተሿሚወቹ  ህዝብን በቅንነት ማገልገል የሚችሉና ከተመደቡበት ቦታ ጋር ተያያዥነት ያለዉ የሙያ ባለቤቶች ሊሆኑ ይገባ ነበርም ብለዋል።