ዶናልድ ያማማቶ ወደ ኤርትራና ኢትዮጵያ ሊጓዙ ነው

በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የአፍሪቃ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ዶናልድ ያማማቶ ወደ ኤርትራ፤ ጅቡቲ እና ኢትዮጵያ ሊጓዙ ነው። ረዳት ምኒስትሩ በአፍሪቃ ቀንድ ለአምስት ቀናት በሚያደርጉት ቆይታ አሜሪካ ከሀገራቱ ጋር ባላት ጥቅሞችና ሥጋቶች ላይ ከከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር ውይይት ያካሒዳሉ ተብሏል።