እስራኤል፤ የኢትዮጵያ አይሁዳዉያንን የመዉሰድ እቅድ

የእስራኤል መንግሥት ኢትዮጵያ ውስጥ ቀርተዋል ያላቸዉን ቤተ እስራኤላዉያን በተቻለ ፍጥነት ወደ ሀገሩ እንደሚወስድ ገለፀ። በኢትዮጵያ ጉብኝታቸዉ ትናንት አዲስ አበባ የሚገኝ አንድ ምኩራብ የተገኙት የእስራኤል የፍትህ ምኒስትር አይሌት ሻከድ እንደገለፁት ሀገራቸዉ ቤተ እስራኤላዉያኑን ወደ መሬቷ የመመለስ ተግባርዋ ቀላል እንደማይሆን ጠቁመዋል።