Re: Coronavirus International updates
Posted: 17 Sep 2020, 09:38
ኮቪድ-19 የህክምና ባለሙያዎችን ይበልጥ እያጠቃ ነው -የአለም ጤና ድርጅት
ኮቪድ-19 ከሌሎች ታማሚዎች በባሰ ሁኔታ የህክምና ባለሙያዎችን ይበልጥ እያጠቃ ስለመሆኑ የአለም ጤና ድርጅትን ጠቅሶ ሮይተርስ ዘገበ።
እንደ የአለም ጤና ድርጅት ከሰባት ታማሚዎች ውስጥ አንዱ የጤና ባለሙያ ሲሆን በአንዳንድ አገሮች ደግሞ ከሶስቱ ሰዎች አንዱ መሆኑ ነው የተገለፀው።
ድርጅቱ በተለይም ቫይረሱን በመከላከል ረገድ ፊት ለፊት የተሰለፉ የህክምና ሰራተኞች የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች እንዳይሆኑና ቫይረሱን ለራሳቸውም ሆነ ለታካሚዎቻቸው ቤተሰቦች እንዳያዛምቱ ራሳቸውን የሚከላከሉባቸው መሳሪያዎች ሊቀርቡላቸው ይገባል ብሏል፡፡
የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም እንደተናገሩት በዓለም አቀፍ ደረጃ ለዓለም ጤና ድርጅት ሪፖርት ከተደረጉት የምርመራ ውጤቶች ውስጥ 14 በመቶ የሚሆኑት የጤና ባለሙያዎችን የሚያመለክት ሲሆን በአንዳንድ ሃገራት ደግሞ ቁጥሩ እስከ 35 በመቶ ይደርሳል ብለዋል ፡፡
ዶ/ር ቴድሮስ የዓለም ህመምተኞች ደህንነት ቀንን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት በመላው አለም የቫይረሱ ተጠቂዎች ቁጥር 30 ሚሊየን የደረሰ ሲሆን የማቾች ቁጥር ደግሞ ወደ 9 መቶ 40 ሺህ ስለመጠጋቱ አስረድተው የተሰበሰበው መረጃ ውስን ስለነበረ ሰዎቹ በበሽታው የተጠቁበትን ቦታ ማወቅ እንዳልተቻለ ተናግረዋል።
አደጋው የባለሙያዎቹ መያዝ ብቻ አይደለም ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ የጤና ባለሙያዎች በየቀኑ ለጭንቀት ፣ ለብስጭት ፣ ለመገለል ፣ ለአድልዎ አለፍ ሲልም ለጥቃት የተጋለጡ መሆናቸው ነው ብለዋል፡፡
የተባበሩት መንግስታት ዓለም አቀፍ የሰራተኞች ድርጅት (አይኤልኦ) ዋና ዳይሬክተር ጋይ ራይደር ሲናገሩ የዓለም ጤና ድርጅት የጤና ባለሙያዎችን በሚመለከት ያወጣው መረጃ አስደንጋጭ እውነታን የያዘ ስለመሆኑ አስረድተዋል ፡፡
የታካሚዎች ደህንነት የጤና ሰራተኞች ደህንነትን የሚጠይቅ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታ መሆኑን ነው ያነሱት።
በአሳዛኝ ሁኔታ ብዙውን ጊዜ ለጤና ባለሙያዎች የሚሰጠው ትኩረት እንደሚያንስ ገልጸዋል።
የዓለም የጤና ድርጅት የአስቸኳይ ጊዜ ሃላፊ ማይክ ሪያን የጤና ባለሙያዎች ሶስት ጊዜ በድግግሞሽ እንደሚጎዱ ሲናገሩ ታማሚዎች በበሽታው አደገኝነት ምክንያት ሲሞቱ ሲያዩ ፣ የስራ ባልደረቦቻቸው ስራ ላይ እያሉ ታመው ሲወድቁ እና ይሄንን ጭንቀትና ቫይረሱን ወደ ቤታቸው ይዘው እንዳይሄዱ በመስጋት ይጎዳሉ ብለዋል።
ዋና መስሪያ ቤቱን ጄኔቫ ያደረገው ዓለም አቀፍ የነርሶች ምክር ቤት የቫይረሱን መከሰት ተከትሎ ከ1 ሺህ በላይ ነርሶች ህይወታቸው እንዳለፈ ዘገባው ጨምሮ ገልጿል ፡፡
ኮቪድ-19 ከሌሎች ታማሚዎች በባሰ ሁኔታ የህክምና ባለሙያዎችን ይበልጥ እያጠቃ ስለመሆኑ የአለም ጤና ድርጅትን ጠቅሶ ሮይተርስ ዘገበ።
እንደ የአለም ጤና ድርጅት ከሰባት ታማሚዎች ውስጥ አንዱ የጤና ባለሙያ ሲሆን በአንዳንድ አገሮች ደግሞ ከሶስቱ ሰዎች አንዱ መሆኑ ነው የተገለፀው።
ድርጅቱ በተለይም ቫይረሱን በመከላከል ረገድ ፊት ለፊት የተሰለፉ የህክምና ሰራተኞች የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች እንዳይሆኑና ቫይረሱን ለራሳቸውም ሆነ ለታካሚዎቻቸው ቤተሰቦች እንዳያዛምቱ ራሳቸውን የሚከላከሉባቸው መሳሪያዎች ሊቀርቡላቸው ይገባል ብሏል፡፡
የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም እንደተናገሩት በዓለም አቀፍ ደረጃ ለዓለም ጤና ድርጅት ሪፖርት ከተደረጉት የምርመራ ውጤቶች ውስጥ 14 በመቶ የሚሆኑት የጤና ባለሙያዎችን የሚያመለክት ሲሆን በአንዳንድ ሃገራት ደግሞ ቁጥሩ እስከ 35 በመቶ ይደርሳል ብለዋል ፡፡
ዶ/ር ቴድሮስ የዓለም ህመምተኞች ደህንነት ቀንን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት በመላው አለም የቫይረሱ ተጠቂዎች ቁጥር 30 ሚሊየን የደረሰ ሲሆን የማቾች ቁጥር ደግሞ ወደ 9 መቶ 40 ሺህ ስለመጠጋቱ አስረድተው የተሰበሰበው መረጃ ውስን ስለነበረ ሰዎቹ በበሽታው የተጠቁበትን ቦታ ማወቅ እንዳልተቻለ ተናግረዋል።
አደጋው የባለሙያዎቹ መያዝ ብቻ አይደለም ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ የጤና ባለሙያዎች በየቀኑ ለጭንቀት ፣ ለብስጭት ፣ ለመገለል ፣ ለአድልዎ አለፍ ሲልም ለጥቃት የተጋለጡ መሆናቸው ነው ብለዋል፡፡
የተባበሩት መንግስታት ዓለም አቀፍ የሰራተኞች ድርጅት (አይኤልኦ) ዋና ዳይሬክተር ጋይ ራይደር ሲናገሩ የዓለም ጤና ድርጅት የጤና ባለሙያዎችን በሚመለከት ያወጣው መረጃ አስደንጋጭ እውነታን የያዘ ስለመሆኑ አስረድተዋል ፡፡
የታካሚዎች ደህንነት የጤና ሰራተኞች ደህንነትን የሚጠይቅ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታ መሆኑን ነው ያነሱት።
በአሳዛኝ ሁኔታ ብዙውን ጊዜ ለጤና ባለሙያዎች የሚሰጠው ትኩረት እንደሚያንስ ገልጸዋል።
የዓለም የጤና ድርጅት የአስቸኳይ ጊዜ ሃላፊ ማይክ ሪያን የጤና ባለሙያዎች ሶስት ጊዜ በድግግሞሽ እንደሚጎዱ ሲናገሩ ታማሚዎች በበሽታው አደገኝነት ምክንያት ሲሞቱ ሲያዩ ፣ የስራ ባልደረቦቻቸው ስራ ላይ እያሉ ታመው ሲወድቁ እና ይሄንን ጭንቀትና ቫይረሱን ወደ ቤታቸው ይዘው እንዳይሄዱ በመስጋት ይጎዳሉ ብለዋል።
ዋና መስሪያ ቤቱን ጄኔቫ ያደረገው ዓለም አቀፍ የነርሶች ምክር ቤት የቫይረሱን መከሰት ተከትሎ ከ1 ሺህ በላይ ነርሶች ህይወታቸው እንዳለፈ ዘገባው ጨምሮ ገልጿል ፡፡