ብልፅግናን ጨምሮ 11 ፓርቲዎች የፖለቲካ አቋማቸውን በያዘ ሰነድ ላይ ስምምነት ተፈራረሙ!
Posted: 23 Sep 2020, 12:34
ብልፅግና ፓርቲን ጨምሮ 11 የኦሮሞ እና የአማራ የፖለቲካ ፓርቲዎች ባለ በ10 ነጥብ የፖለቲካ አቋማቸውን በያዘ ሰነድ ላይ ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱን የተፈራረሙት ፓርቲዎች ብልፅግና ፓርቲ፣ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ፣ የአማራ ህልውና ለኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት፣ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር፣ የመላው አማራ ህዝብ ፓርቲ፣ ነፀብራቅ አማራ ድርጅት፣ የኦሮሞ ነፃነት ፌዴራሊስት ኮንግረስ ፓርቲ፣ የአማራ ዴሞክራሲ ኃይል ንቅናቄ እና የመላው አማራ ህዝብ ድርጅት ናቸው። ፓርቲዎቹ ከስምምነት ላይ ደርሰው
የተፈራረሙባቸው ነጥቦች ደግሞ የሚከተሉት ናቸው፡-
1. የሀገራችንን የፖለቲካ ችግሮችን ለመፍታት ሁሉን አካታች የሆነ ቀጣይ ሀገራዊ ውይይትና ድርድር ማካሄድ፤
2. ጥርጣሬ፣ መከፋፈል፣ እርስ በርስ መቃረን፣ አንዱ የሌላውን ስም ከማጥፋት እንዲሁም ሕዝብ ለሕዝብ ከሚያጋጩና ከሚያቃርኑ ድርጊቶች መቆጠብ፣
3. ሀገራዊ የህዝብ ቆጠራ ተአማኒነትና ተቀባይነት ባለው አሠራር በማካሄድ የሁሉም የሀገሪቱ ብሔር ብሐረሰቦች የሕዝብ ብዛት በአግባቡ ተቆጥሮ እንዲታወቅ ማድረግ፤ በትክክል እንዲቆጠር፣ የከዚህ በፊት ግድፈቶች የሚያርምና የማይደገምበት መሆኑን ማረጋገጥ፤
4. በሀገራችን ዲሞክራሲያዊ ስርዓትን መገንባት፣ የግልና የቡድን መብቶችን ማስከበርና በየጊዜውና በየደረጃው ነጻና ፍትሐዊ ምርጫን ማካሄድ፣
5. በኢትዮጵያ የታሪክ አቀራረብ የታሪክ አንጓዎችን ተከትሎ ከሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች በተወጣጡ የታሪክ ምሁራን የሀገሪቱን ህዝቦች ግንኙነትና ታሪክ ጥናት እንዲካሄድ፤ የብሔረሰቦች ጥናት ተቋም እንዲቋቋም፣
6. በኦሮሞና አማራ ክልሎች የሚኖሩ የሁሉም ህዝቦች አባላት ደህንነትና መብቶች እንዲከበሩ፤
7. በሀገራችን የሁሉም አካባቢዎች ሰላምና ፀጥታ፣ ህግና ፍትህ ማስፈን፤ ከየቦታው ያለአግባብ የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቀያቸውና ኑሯቸው እንዲመለሱ እንዲደረግ፤
8. ሀገሪቱ የምትተዳረርበት ሕገ መንግሥት ሁሉን አሳታፊ በሆነ መንገድ እንዲሻሻል ማድረግ
9. በሀገሪቱ ዘላቂና ፍትሀዊ የኢኮኖሚ ልማት ማጎልበት፤ የህዝቦቻችንን ፍትሀዊ የኢኮኖሚና የሀብት ተጠቃሚነት ማረጋገጥ፤
10. የተለያዩ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቶችንና ትብብሮችን የሚያጠናክሩ ዝግጅቶችን በጋራ ማዘጋጀት ናቸው።
ፓርቲዎቹ ለ10 ወራት ያህል በተለያዩ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ሲወያዩ ቆይተው በ10 ነጥቦች ላይ ተስማምተዋል።
የውይይታቸው መነሻ ባለፈው ዓመት በሁለቱ ክልሎች በሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ግጭቶች መከሰታቸውና ከዚህ ጀርባ የፖለቲካ ተዋንያን አሉ በሚል ግንዛቤ ሁኔታውን ለማርገብ መሆኑ ተገልጿል።
ከሁለቱም አካላት ገለልተኛ ሰዎች ተመርጠው ሲያወያዩ መቆየታቸውም ተገልጿል።
ፓርቲዎቹ ዛሬ ውይይት ባካሄዱበት የጋራ የፖለቲካ አቋመማቸውን በያዘ ሰነድ ላይ በሸራተን አዲስ ተፈራርመዋል።
የፓርቲዎቹን ውይይት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ባለፈው ዓመት ሕዳር ላይ ማስጀመራቸው ይታወሳል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
ምንጭ፦ EBC
የተፈራረሙባቸው ነጥቦች ደግሞ የሚከተሉት ናቸው፡-
1. የሀገራችንን የፖለቲካ ችግሮችን ለመፍታት ሁሉን አካታች የሆነ ቀጣይ ሀገራዊ ውይይትና ድርድር ማካሄድ፤
2. ጥርጣሬ፣ መከፋፈል፣ እርስ በርስ መቃረን፣ አንዱ የሌላውን ስም ከማጥፋት እንዲሁም ሕዝብ ለሕዝብ ከሚያጋጩና ከሚያቃርኑ ድርጊቶች መቆጠብ፣
3. ሀገራዊ የህዝብ ቆጠራ ተአማኒነትና ተቀባይነት ባለው አሠራር በማካሄድ የሁሉም የሀገሪቱ ብሔር ብሐረሰቦች የሕዝብ ብዛት በአግባቡ ተቆጥሮ እንዲታወቅ ማድረግ፤ በትክክል እንዲቆጠር፣ የከዚህ በፊት ግድፈቶች የሚያርምና የማይደገምበት መሆኑን ማረጋገጥ፤
4. በሀገራችን ዲሞክራሲያዊ ስርዓትን መገንባት፣ የግልና የቡድን መብቶችን ማስከበርና በየጊዜውና በየደረጃው ነጻና ፍትሐዊ ምርጫን ማካሄድ፣
5. በኢትዮጵያ የታሪክ አቀራረብ የታሪክ አንጓዎችን ተከትሎ ከሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች በተወጣጡ የታሪክ ምሁራን የሀገሪቱን ህዝቦች ግንኙነትና ታሪክ ጥናት እንዲካሄድ፤ የብሔረሰቦች ጥናት ተቋም እንዲቋቋም፣
6. በኦሮሞና አማራ ክልሎች የሚኖሩ የሁሉም ህዝቦች አባላት ደህንነትና መብቶች እንዲከበሩ፤
7. በሀገራችን የሁሉም አካባቢዎች ሰላምና ፀጥታ፣ ህግና ፍትህ ማስፈን፤ ከየቦታው ያለአግባብ የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቀያቸውና ኑሯቸው እንዲመለሱ እንዲደረግ፤
8. ሀገሪቱ የምትተዳረርበት ሕገ መንግሥት ሁሉን አሳታፊ በሆነ መንገድ እንዲሻሻል ማድረግ
9. በሀገሪቱ ዘላቂና ፍትሀዊ የኢኮኖሚ ልማት ማጎልበት፤ የህዝቦቻችንን ፍትሀዊ የኢኮኖሚና የሀብት ተጠቃሚነት ማረጋገጥ፤
10. የተለያዩ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቶችንና ትብብሮችን የሚያጠናክሩ ዝግጅቶችን በጋራ ማዘጋጀት ናቸው።
ፓርቲዎቹ ለ10 ወራት ያህል በተለያዩ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ሲወያዩ ቆይተው በ10 ነጥቦች ላይ ተስማምተዋል።
የውይይታቸው መነሻ ባለፈው ዓመት በሁለቱ ክልሎች በሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ግጭቶች መከሰታቸውና ከዚህ ጀርባ የፖለቲካ ተዋንያን አሉ በሚል ግንዛቤ ሁኔታውን ለማርገብ መሆኑ ተገልጿል።
ከሁለቱም አካላት ገለልተኛ ሰዎች ተመርጠው ሲያወያዩ መቆየታቸውም ተገልጿል።
ፓርቲዎቹ ዛሬ ውይይት ባካሄዱበት የጋራ የፖለቲካ አቋመማቸውን በያዘ ሰነድ ላይ በሸራተን አዲስ ተፈራርመዋል።
የፓርቲዎቹን ውይይት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ባለፈው ዓመት ሕዳር ላይ ማስጀመራቸው ይታወሳል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
ምንጭ፦ EBC