Page 1 of 1
PP's "cyber army" exposed by BBC Investigaive Report
Posted: 19 Apr 2024, 21:23
by Revelations
And it has been quite a while since we exposed the PP "cyber army" aka a few devoted cadres right here on this forum!
Please wait, video is loading...
Re: PP's "cyber army" exposed by BBC Investigaive Report
Posted: 19 Apr 2024, 22:30
by Revelations
አበል የሚታሰብላቸው ተቀጣሪ ‘የሚዲያ ሠራዊት’ አባላት
ከ15 ዓመታት በላይ በፌደራል መንግሥት ተቋማት የኮሚዩኒኬሽን ኃላፊነት የሠሩ አንድ ምንጭ፤ የፓርቲ አባላትን በመጠቀም በዘመቻ መልክ የመንግሥትን ፕሮፓጋንዳ በፌስቡክ ላይ የማሠራጨት ሀሳብ የቀድሞው ገዢ የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢሕአዴግ) በመጨረሻዎቹ የሥልጣን ዓመታት ላይ በዕቅድ ደረጃ ተዘጋጅቶ የነበረ ጉዳይ እንደሆነ ለቢቢሲ ገልጸዋል።
መንግሥት ላይ የሚደረጉ ተቃውሞዎች እየበረቱ በመጡበት በ2008 ዓ.ም.፤ የቀድሞው የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ይህንን የተመለከተ ሥልጠና ለመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ባለሙያዎች ሰጥቶ እንደነበር አስታውሰዋል። ይሁንና ኢሕአዴግን የመሠረቱት አራት ፓርቲዎች ተቃውሞዎቹን በተመለከተ ያላቸው አቋም እየተለያየ በመምጣቱ በታሰበው ልክ ዕቅዱን መተግበር አለመቻሉን ምንጩ አስረድተዋል።
በአሁኑ ጊዜ የሚታየው የፌስቡክ ዘመቻ አተገባበር ከስምንት ዓመት በፊት ተዘጋጅቶ ከነበረው ዕቅድ ጋር ተመሳሳይነት እንዳለው የሚያነሱት ምንጩ፤ ብልፅግና ፓርቲ እና የመንግሥት አመራሮች በወቅቱ የተዘጋጀው ዕቅድ መተግበር ላይ “ተሳክቶላቸዋል” ብለው እንደሚያምኑም ጠቅሰዋል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ መንግሥት ወደ ሥልጣን ከመጣ እና ብልፅግና ፓርቲ ከተመሠረተ በኋላም የቀጠለው የሚዲያ ሠራዊትን ተጠቅሞ ፕሮፓጋንዳ የማሠራጨት ዕቅድ ብቻ አልነበረም። የማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምን እና ሥርዓተ ቀመርን (አልጎሪዝም) የተመለከቱ ሥልጠናዎች አሁንም በብልፅግና ፓርቲ የተለያዩ መዋቅሮች ይሰጣሉ።
ለፓርቲ አባላት እና የኮሚዩኒኬሽን ባለሙያዎች የሚሰጡት የእነዚህ ሥልጠናዎች አንዱ ትኩረት “በሀገሪቱ የሚከናወኑ የልማት ፕሮጀክቶቻችንን” የተመለከቱ “መረጃዎችን ለሕዝብ ማድረስ” የሚል ነው።
የብልፅግና ፓርቲ ዋና ፅህፈት ቤት ለቢቢሲ በሰጠው ምላሽ ላይ “የማኅበራዊ ሚዲያ ምንነትና ፋይዳ፣ የመተግበሪያዎቹ አሰራርና በመተግበሪያዎቹ ሃሳብን እንዴት ለብዙኃን ማድረስ እንደሚቻል” ለአመራሮቹ እና ለአባላቱ ሥልጠናዎችን እንደሚሰጥ ጠቅሷል።
ፓርቲው፤ “ይህ ደግሞ በየትኛውም የዓለም ክፍል ያለ የፖለቲካ ማኅበር ሁሉ ሊያደርገው የሚችልና የሚገባ እንደሆነ ያምናል” ሲል ይህንን ዓይነቱ ጉዳይ የተለመደ አሠራር መሆኑን ገልጿል።
በመንግሥት እና ፓርቲ የፌስቡክ ገጾች ላይ ተከታይ እና ተሳታፊዎችን የማብዛት ጥረት፤ በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ ሁለት ቢሮዎች ላይክ፣ ኮሜንት እና ሼር የሚያደርጉ ሰዎችን እስከመቅጠር እንዳደረሰ ሁለት የቢሮዎቹ ምንጮች ለቢቢሲ ገልጸዋል።
በዚህ ዓይነት መልኩ የፌስቡክ ገጻቸውን ተሳትፎ ለማብዛት እየሞከሩ እንደሆነ የተጠቀሱት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ እንዲሁም ፐብሊክ ሰርቨስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ናቸው። ቢቢሲ በሁለት ቢሮዎች የፌስቡክ ልጥፎች ላይ ያደረገው የዳታ ትንተና ከምንጮች ከተገኘው መረጃ ጋር ተመሳሳይ ነው።
ይህንን ጉዳይ አስመልክቶ ቢቢሲ ጥያቄ ያቀረበለት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ፤ በቢሮው የፌስቡክ ገጽ ላይ ተሳትፎ ለማድረግ “የተቀጠሩ እና ክፍያ የሚያገኙ ግለሰቦች አሉ” መባሉን አስተባብሏል።
ቢሮው የሶሻል ሚዲያ አጠቃቀምን በተመለከተ ለወጣቶች ሥልጠና እንደሚሰጥ ለቢቢሲ የተናገሩት የቢሮው የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ መሃሪ ተመስገን፤ ይህንን ሥልጠና የወሰዱ ግለሰቦች በቢሮው ገጽ ላይ ተሳትፎ እንዳላቸው ገልጸዋል።
አቶ መሃሪ፤ “ከእኛ ቢሮ ጋር የሚሠሩ ወጣቶች እና የስፖርት ቤተሰቦች የተቋሙን ፔጅ በመከታተል የሚለቀቁ መረጃዎች ላይ የራሳቸውን ላይክም፣ ኮሜንትም እንዲያደርጉ የተለያዩ ሥልጠናዎችን እንሰጣለን። ሥልጠናውን ከወሰዱ ሰዎች ውስጥ አንዳንዶቹ በተደጋጋሚ [ኮሜንት] እያደረጉ ሊሆን ይችላል” ብለዋል።
ተመሳሳይ ጥያቄ የቀረበላቸው የፐብሊክ ሰርቨስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ጣሰው ገብሬ ደግሞ ይህ ዓይነቱ ተግባር ስለመኖሩ “መረጃ እንደሌላቸው” ተናግረዋል። ኃላፊው ጉዳዩን አጣርተው መረጃ እንደሚሰጡ ቃል የገቡ ቢሆንም፣ ከዚያ በኋላ ከቢቢሲ የተደረገላቸውን ተደጋጋሚ የስልክ ጥሪ አልመለሱም።
ቢቢሲ ከምንጮች ያገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ይህንን ተግባር ለመፈጸም "የተቀጠሩት" 11 ግለሰቦች ተሳትፎ የሚያደርጉት በሁለቱም ቢሮዎች የፌስቡክ ገጾች ላይ ነው። ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው አንድ ምንጭ ግለሰቦቹ የብልፅግና ፓርቲ አባል የሆኑ እንዲሁም በወረዳዎች እና በክፍለ ከተሞች ላይ የኮሚዩኒኬሽን ባለሙያ ሆነው መደበኛ ሥራ የሚያከናውኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ምንጩ ጨምረውም “አንድ ሰው እስከ ስምንት እና አስር የፌስቡክ አካውንት አለው። በቀኑ የሚከታተሉት የእኛን ገጽ ነው። ኮሜንት፣ ሼር ሲያደርጉ የተጻፈውን ያነቡትና በእሱ ላይ ተመርኩዘው የቢሮውን ሥራ የሚደግፍ ኮሜንት ይሰጣሉ። የእኛን ልጥፍ ወስደው በአስሩ ፔጃቸው ላይ ሼር ያደርጉታል ማለት ነው” ይላሉ። ግለሰቦቹ ለዚህ ተግባራቸው “በአበል መልክ” ክፍያ እንደሚያገኙ ምንጮቹ ገልጸዋል።
ቢቢሲ፤ የፌስቡክ ይዘቶች መከታተያ የሆነውን “ክራውድ ታንግል” ተጠቅሞ ያገኘው ዳታ እንደሚያመለክተው ከኅዳር እና ታኅሣሥ ወራት ጀምሮ የሁለቱ ቢሮዎች ገጾች ልጥፎች ላይ የሚሳተፉ አካውንቶች እና ገጾች ቁጥር በከፍተኛ መጠን ጨምሯል። ይህ ወቅት ምንጮች የግለሰቦቹ ቅጥር እንደተፈጸመ ከገለጹት ጊዜ ጋር ተመሳሳይ ነው።
አብዛኛውን ጊዜ በገጾቹ ልጥፎች ላይ ኮሜንት የሚያደርጉት ተመሳሳይ አካውንቶች ሲሆኑ፣ እነዚሁ አካውንቶች በሁለቱም ቢሮዎች ገጽ ላይ እንደሚሳተፉ ቢቢሲ አረጋግጧል። ቢቢሲ በዚህ ተግባር ላይ የሚሳተፉ እና ከሁለት ግለሰቦች ጋር ግንኙነት ያላቸውን 16 አካውንት እና ገጾች ለይቷል።
የዲጂታል ሰብአዊ መብቶች ተመራማሪው ዶ/ር ዮሃንስ፤ ከመንግሥት ጋር በተያያዙ ልጥፎች ላይ በተደራጀ መልኩ በብዛት ኮሜንቶችን መስጠት “ሀሳብን በነጻነት መግለፅ ሳይሆን ሌሎችን ማሸማቀቅ ነው” ይላሉ። ይህ አይነቱ እንቅስቃሴ “ተቃዋሚዎችን ማፈን፣ በንቃት የሚጽፉ ሰዎችን ከመድረኩ እንዲወጡ ማድረግ እንዲሁም በነጻነት የመናገር እና መረጃ የማግኘት መብትን መገደብ” እንደሚያስከትል ጠቅሰዋል።
አቶ መሃሪ፤ “ከእኛ ቢሮ ጋር የሚሠሩ ወጣቶች እና የስፖርት ቤተሰቦች የተቋሙን ፔጅ በመከታተል የሚለቀቁ መረጃዎች ላይ የራሳቸውን ላይክም፣ ኮሜንትም እንዲያደርጉ የተለያዩ ሥልጠናዎችን እንሰጣለን። ሥልጠናውን ከወሰዱ ሰዎች ውስጥ አንዳንዶቹ በተደጋጋሚ [ኮሜንት] እያደረጉ ሊሆን ይችላል” ብለዋል።
ተመሳሳይ ጥያቄ የቀረበላቸው የፐብሊክ ሰርቨስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ጣሰው ገብሬ ደግሞ ይህ ዓይነቱ ተግባር ስለመኖሩ “መረጃ እንደሌላቸው” ተናግረዋል። ኃላፊው ጉዳዩን አጣርተው መረጃ እንደሚሰጡ ቃል የገቡ ቢሆንም፣ ከዚያ በኋላ ከቢቢሲ የተደረገላቸውን ተደጋጋሚ የስልክ ጥሪ አልመለሱም።
ቢቢሲ ከምንጮች ያገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ይህንን ተግባር ለመፈጸም "የተቀጠሩት" 11 ግለሰቦች ተሳትፎ የሚያደርጉት በሁለቱም ቢሮዎች የፌስቡክ ገጾች ላይ ነው። ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው አንድ ምንጭ ግለሰቦቹ የብልፅግና ፓርቲ አባል የሆኑ እንዲሁም በወረዳዎች እና በክፍለ ከተሞች ላይ የኮሚዩኒኬሽን ባለሙያ ሆነው መደበኛ ሥራ የሚያከናውኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ምንጩ ጨምረውም “አንድ ሰው እስከ ስምንት እና አስር የፌስቡክ አካውንት አለው። በቀኑ የሚከታተሉት የእኛን ገጽ ነው። ኮሜንት፣ ሼር ሲያደርጉ የተጻፈውን ያነቡትና በእሱ ላይ ተመርኩዘው የቢሮውን ሥራ የሚደግፍ ኮሜንት ይሰጣሉ። የእኛን ልጥፍ ወስደው በአስሩ ፔጃቸው ላይ ሼር ያደርጉታል ማለት ነው” ይላሉ። ግለሰቦቹ ለዚህ ተግባራቸው “በአበል መልክ” ክፍያ እንደሚያገኙ ምንጮቹ ገልጸዋል።
ቢቢሲ፤ የፌስቡክ ይዘቶች መከታተያ የሆነውን “ክራውድ ታንግል” ተጠቅሞ ያገኘው ዳታ እንደሚያመለክተው ከኅዳር እና ታኅሣሥ ወራት ጀምሮ የሁለቱ ቢሮዎች ገጾች ልጥፎች ላይ የሚሳተፉ አካውንቶች እና ገጾች ቁጥር በከፍተኛ መጠን ጨምሯል። ይህ ወቅት ምንጮች የግለሰቦቹ ቅጥር እንደተፈጸመ ከገለጹት ጊዜ ጋር ተመሳሳይ ነው።
አብዛኛውን ጊዜ በገጾቹ ልጥፎች ላይ ኮሜንት የሚያደርጉት ተመሳሳይ አካውንቶች ሲሆኑ፣ እነዚሁ አካውንቶች በሁለቱም ቢሮዎች ገጽ ላይ እንደሚሳተፉ ቢቢሲ አረጋግጧል። ቢቢሲ በዚህ ተግባር ላይ የሚሳተፉ እና ከሁለት ግለሰቦች ጋር ግንኙነት ያላቸውን 16 አካውንት እና ገጾች ለይቷል።
የዲጂታል ሰብአዊ መብቶች ተመራማሪው ዶ/ር ዮሃንስ፤ ከመንግሥት ጋር በተያያዙ ልጥፎች ላይ በተደራጀ መልኩ በብዛት ኮሜንቶችን መስጠት “ሀሳብን በነጻነት መግለፅ ሳይሆን ሌሎችን ማሸማቀቅ ነው” ይላሉ። ይህ አይነቱ እንቅስቃሴ “ተቃዋሚዎችን ማፈን፣ በንቃት የሚጽፉ ሰዎችን ከመድረኩ እንዲወጡ ማድረግ እንዲሁም በነጻነት የመናገር እና መረጃ የማግኘት መብትን መገደብ” እንደሚያስከትል ጠቅሰዋል።
Re: PP's "cyber army" exposed by BBC Investigaive Report
Posted: 19 Apr 2024, 23:00
by Revelations
በአዲስ አበባ ከተማ ከወረዳ እስከ ክፍለ ከተማ የሚገኙ አመራሮች በማኅበራዊ ሚዲያ ዘመቻዎች ላይ ይሳተፋሉ። በከተማዋ ከ500 በላይ የክፍለ ከተማ እና ከ3,500 በላይ የወረዳ አመራሮች አሉ።
Re: PP's "cyber army" exposed by BBC Investigaive Report
Posted: 19 Apr 2024, 23:27
by Revelations
ቢቢሲ በተመለከታቸው የቴሌግራም እና ዋትስአፕ ግሩፖች ውስጥ የሚገኙ የወረዳ አመራሮች እና የሚዲያ ሰራዊት አባላት ፌስቡክ ላይ ፖስት፣ ኮሜንት ወይም ሼር ማደረጋቸውን የሚያረጋግጥ ስክሪንሻት እንዲልኩ ይጠየቃሉ።
Re: PP's "cyber army" exposed by BBC Investigaive Report
Posted: 19 Apr 2024, 23:54
by Revelations
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፓርላማ በቀረቡበት ዕለት 93 የተዘጋጁ ኮሜንቶች ለዋትስአፕ ግሩፕ አባላቱ ተልከዋል። ከስብሰባው መጠናቀቅ በኋላ ደግሞ የጠ/ሚ ዐቢይን ምስል እና ንግግር የያዙ 26 ግራፊክስ ምሥሎችን በግሩፑ ላይ ተለቅቀዋል።
Re: PP's "cyber army" exposed by BBC Investigaive Report
Posted: 20 Apr 2024, 00:04
by Revelations
የዋትስአፕ ግሩፑ አስተዳዳሪ የላካቸው ፅሁፎች በአቶ ታዬ የፌስቡክ ገፅ ላይ ቢያንስ 365 ጊዜ በተለያዩ አካውንቶች ኮሜንት መደረጋቸው ቢቢሲ አረጋግጧል።
Re: PP's "cyber army" exposed by BBC Investigaive Report
Posted: 20 Apr 2024, 00:15
by Revelations
በሁለት ሰዎች የተከፈቱት እነዚህ አካውንቶች በአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ እንዲሁም ፐብሊክ ሰርቨስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ የፌስቡክ ገጾች ላይ በተደጋጋሚ ኮሜንት ያደርጋሉ።
Re: PP's "cyber army" exposed by BBC Investigaive Report
Posted: 20 Apr 2024, 00:26
by Revelations
በዋትስአፕ ግሩፑ ላይ የተላኩት ምስሎች “ጽንፈኛው” እና “አሜሪካዊው” የሚሉ ቅፅሎችን በመጠቀም የአቡነ ጴጥሮስን “መኮብለል” የሚገልፁ ናቸው።
ከሦስት ወራት በፊት ጥር 2/2016 ዓ.ም. ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ገደማ ጀምሮ “አቡነ ጴጥሮስ ከሀገር ኮበለሉ” የሚሉ ልጥፎች በበርካታ የኢትዮጵያውያን የፌስቡክ አካውንቶች እና ገጾች መሠራጨት ጀመሩ።
በፎቶ እና ጽሁፍ ከተቀናበረ ምስል ጋር የተሠራጩት እነዚህ ልጥፎች ፌስቡክ ላይ የወጡት፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ አቡነ ጴጥሮስ ከአዲስ አበባ ወደ አሜሪካ መጓዛቸውን ተከትሎ ነበር።
የኒው ዮርክ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የሆኑት አቡነ ጴጥሮስ ከሀገር የወጡት፤ “ይፋዊ የሆነውን መደበኛ የአሠራር ሥርዓት ተከትለው” እንደሆነ ቢቢሲ ከቤተ ክርስቲያኗ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
በዕለቱ የተሠራጩት ሦስት ዋነኛ ጽሁፎች “ሰበር መረጃ፤ አቡነ ጴጥሮስ ከሀገር ኮበለሉ”፣ “አሜሪካዊው አቡነ ጴጥሮስ ከሀገር ኮብልለዋል!” እና “ከአሜሪካዊ አቡነ ጴጥሮስ ኩብለላ ጀርባ ያሉ እውነታዎች!” የሚል መግቢያ ያላቸው ናቸው።
ጽሁፎቹ አቡነ ጴጥሮስን፤ “በቤተ ክህነት ውስጥ ህቡዕ የፖለቲካ አደረጃጀት በመምራት” እና “የቤተክህነት ሃብት የሆነ በርካታ ገንዘብ እና ንብረት ይዞ በመጥፋት” ይከስሳሉ።
ከሦስቱ ጽሁፎች ውስጥ በብዛት የተሠራጨው “ሰበር መረጃ፤ አቡነ ጴጥሮስ ከሀገር ኮበለሉ” የሚለው ሲሆን፣ ይህ ጽሁፍ በጥር 2 እና 3/2016 ዓ.ም. ብቻ ቢያንስ 1,004 ጊዜ በተለያዩ የፌስቡክ አካውንት እና ገጾች እንደተለጠፈ ቢቢሲ አረጋግጧል። ከግራፊክስ ምስሎች ጋር የተለጠፈው ይህ ጽሁፍ፤ ጥር ሁለት ቀን ብቻ ይህ ቢያንስ 898 ጊዜ ፌስቡክ ላይ ተጋርቷል።
አቡነ ጴጥሮስ “ኮብልለዋል” በሚል ፌስቡክ ላይ ከተሠራጩት ልጥፎች ውስጥ አብዛኛዎቹ “#ፅንፈኝነት_ይውደም” እና “#መከላከያ_የሀገር_ጋሻ” የሚል ሀሽታግ ተያይዞባቸዋል።
Re: PP's "cyber army" exposed by BBC Investigaive Report
Posted: 20 Apr 2024, 07:46
by Revelations
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የፓርላማ ውሏቸውን በፌስቡክ ገፃቸው ሲያሠራጩ ቢያንስ 43 ጊዜ አወዳሽ ኮሜንቶችን ሰጥቶ የነበረው ይህ አካውንት በሜታ ተወግዷል።