Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Za-Ilmaknun
Member
Posts: 4102
Joined: 15 Jun 2018, 17:40

የአፍሪካ ኅብረት ከ6 ሚሊዮን ዶላር በላይ ሊጭበረበር እንደነበር አስታወቀ:-ተጠርጥረው ተያዙቀሲስ በላይ መኮንን

Post by Za-Ilmaknun » 01 May 2024, 13:45

የአፍሪካ ኅብረት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሚገኘው የባንክ ተቀማጩ ላይ ከ6 ሚሊዮን ዶላር በላይ በማጭበርበር ወጪ ሊደረግ ሲል ማዳኑን ትላንት ማክሰኞ አስታውቋል።

ሰኞ ሚያዚያ 7 ቀን 2016 ዓ/ም ገንዘቡን ሊያወጣ የነበረውና በስም ያልተጠቀሰው ግለሰብ የኅብረቱ ተቀጣሪ እንዳልሆነም አስታውቋል።

ግለሰቡ ለግንባታ እና ለውሃ ጒድጓድ ቁፋሮ ተከፋይ በሚል ባቀረባቸው የተጭበረበሩ ሰነዶች አማካይነት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአፍሪካ ኅብረት ቅርንጫፍ ሚያዚያ 7 ቀን 2016 ሊያወጣ ሞክሮ እንደነበረ አስታውቋል።

የኢትዮጵያ የፀጥታ ባለሥልጣናት ወዲያውኑ ስለ ሁኔታው እንዲያውቁ መደረጉን እና ግለሰቡ በምርመራ አሰራር ደንብ መሠረት ተለይተው መያዛቸውን ኅብረቱ ማስታወቁን የኤኤፍፒ ዘገባ አመልክቷል።

ተጠርጥረው ተያዙ የተባሉት ግለሰብ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ጠቅላይ ቤተክህነት ም/ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን :roll: መሆናቸውንና ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት መቅረባቸውንም የአሜሪካ ድምፅ የአማርኛ አገልግሎት ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ ሚያዚያ 16፣ 2016 ጠበቃቸውን አነጋግሮ መዘገቡ ይታወሳል።

ፍርድ ቤቱም የተጠርጣሪውን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ በማድረግ ለፖሊስ የስምንት ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፈቅዷል፡፡

https://amharic.voanews.com/a/au-bank-f ... 93590.html

Za-Ilmaknun
Member
Posts: 4102
Joined: 15 Jun 2018, 17:40

Re: የአፍሪካ ኅብረት ከ6 ሚሊዮን ዶላር በላይ ሊጭበረበር እንደነበር አስታወቀ:-ተጠርጥረው ተያዙቀሲስ በላይ መኮንን

Post by Za-Ilmaknun » 01 May 2024, 14:01

የቀሲስ በላይ የባንክ ማጭበርበር የደህንነት አቋሜን እንድፈትሽ አድርጓል ሲል አፍሪካ ሕብረት አሳወቀ

አፍሪካ ኅብረት፣ ከኹለት ሳምንት በፊት በግቢው ውስጥ በሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ ለግንባታና ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ በሚል በተጭበረበሩ ሰነዶች ሊወጣ የነበረው ገንዘብ 6 ሚሊዮን ዶላር እንደነበር ዛሬ ባወጣው መግለጫ ገልጧል።

ኅብረቱ የተደረገበትን የማጭበርበር ሙከራ የፋይናንስ ሠራተኞቹ ማክሸፋቸውን ገልጦ፣ ሙከራው ግን በከፍተኛ አንክሮ የምመለከተው ክስተት ነው ብሏል። ኅብረቱ፣ የማጭበርበር ሙከራው በደኅንነት ሥርዓቱ ላይ ፍተሻ ለማድረግ በር እንደከፈተለትም ጠቅሷል።

በባንክ ሒሳቡ ላይ ወደፊት የማጭበርበር ድርጊቶች እንዳይፈጸሙ ለመከላከል ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በትብብር እየሠራ መኾኑንም ኅብረቱ አስታውቋል።

Za-Ilmaknun
Member
Posts: 4102
Joined: 15 Jun 2018, 17:40

Re: የአፍሪካ ኅብረት ከ6 ሚሊዮን ዶላር በላይ ሊጭበረበር እንደነበር አስታወቀ:-ተጠርጥረው ተያዙቀሲስ በላይ መኮንን

Post by Za-Ilmaknun » 03 May 2024, 13:13

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በእነ ቀሲስ በላይ መኮንን ላይ የክስ መመሥረቻ 15 ቀናት ፈቀደ:

በሐሰተኛ ሰነድ ከአፍሪካ ኅብረት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ገንዘብ ለማውጣት በመሞከር የተጠረጠሩት ቀሲስ በላይ መኮንን እና ሌሎች ሁለት ተጠርጣሪዎች ላይ የክስ መመሥረቻ 15 ቀናት በፍርድ ቤት መፈቀዱን ጠበቃ አቶ ቱሊ ባይሳ ለቢቢሲ ተናገሩ።

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ይህንን ውሳኔ ያስተላለፈው ዛሬ ሐሙስ 24/ 2016 ዓ. ም. ረፋድ ላይ በነበረው የፍርድ ቤት ውሎው ነው።

ቀሲስ በላይ እንዲሁም አብረው በቁጥጥር ሥር የዋሉት አጃቢያቸው እና ሹፌራቸው ዛሬ ለሦስተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረቡት፤ ባለፈው ሳምንት በነበረው ችሎት ፍርድ ቤቱ ለመርማሪ ፖሊስ ስምንት ተጨማሪ የምርመራ ቀናት በመፍቀዱ ነው።
https://www.bbc.com/amharic/articles/cgrjgnn5z6go

Post Reply