Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum



Axumezana
Senior Member
Posts: 13946
Joined: 27 Jan 2020, 23:15

Re: "ቀኑ ወልቃይት ነው ጠገዴ ወራቱ፣ መቁጠሪያው ጎንደር ነው አመተ ምህረቱ!"

Post by Axumezana » 02 May 2024, 00:54

ተከዘ፥ ታስረዋል፥ ከትግረዋይ፥ ጋራ፥
ሊፈታው፥ አይችል፥የጎንደር፥ ደብተራ፥



Revelations
Senior Member+
Posts: 33813
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

Re: "ቀኑ ወልቃይት ነው ጠገዴ ወራቱ፣ መቁጠሪያው ጎንደር ነው አመተ ምህረቱ!"

Post by Revelations » 02 May 2024, 17:20

የወረራ ዝግጅት!

ራያን የወረረው ትህነግ ጠለምትንና ወልቃይትን ለመውረር ቅድመ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል። በዚህም መሰረት በሱዳን በኩል፣ አርሚ 11 ጠለምትን ለመውረር፣ አርሚ 17 ወልቃይትን ለመውረር ዝግጅት ላይ ነው፣ አርሚ 35 ከአክሱም ወደ ሽሬ የተንቀሳቀሰ ሲሆን ጥቅምት 24 መከላከያን የመቱበትን ማስታወሻ ያደረጉት "አርሚ 24" ደግሞ ራያን የወረረው ነው።

ይህ በሆነበት ብልፅግና የአማራ አስተዳደሮችን በሕገወጥ መልኩ አፍርሶ በተፈናቃይ ስም የወረራ በር እየከፈተና እያገዘ ይገኛል። እንደ ገለልተኛ "ትጥቅ መፍታት አለባቸው" እያለ የሚቀልደውም ዝግጅታቸውን ስለማያውቅ አይደለም። ማዘናጊያ ነው።

በሌላ በኩል በተቃዋሚም ሆነ በሌላ ስም ትህነግ ጋር ስምምነት ለመፈፀም የሚደረግን ሂደት የህዝብ ለህዝብ እያስመሰለ፣ የትህነግን ወረራ የሚያድበሰብስም የትህነግና ብልፅግናን የጓዳ ውልና የወረራ አላማ የሚያስፈፅም የአማራ ጠላት መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል።

Getachew shiferaw


Post Reply