ህገወጥ የገንዘብ ዝውውርን መግታት የሚቻለው መንገድ በመዝጋት ሳይሆን የሌቦቹን የባንክ አካውንት በመዝጋት ነው። በዚህ መሠረት በጎረቤት ሀገራት እና በሀገር ውስጥ የሚገኙ የገንዘብ አዘዋዋሪዎች፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ አየርመንገድ የበረራ አስተናጋጆች አማካኝነት የሚዘዋወረው ገንዘብ ከተወረሰና በዚህ ተግባር የተሰማሩት ሰዎች በህግ ቁጥጥር ስር ከዋሉ፤
አንደኛ፦ ወደ ኢትዮጵያ የሚላከው ገንዘብ በህጋዊ መንገድ በባንኮች በኩል ይሆናል።
ሁለተኛ፦ ወደ ውጪ የሚላከው ገንዘብ በህጋዊ መንገድ በባንኮች በኩል ይሆናል።
ሦስተኛ፦ በህገወጥ መንገድ የሚንቀሳቀስ ገንዘብና የጥቁር ገበያ ምንዛሬ ይቀንሳል
አራተኛ፦ በኢትዮጵያ ባንኮች ውስጥ የተሻለ የውጪ ምንዛሬ አቅርቦት ይገኛል።
አምስተኛ፦ የውጪ ምንዛሬ በብሔራዊ ባንክ ተመን መሠረት ሲሆን ከውጪ የሚገቡ ምርቶች ዋጋ ይቀንሳል።
ስድስተኛ፦ ህገወጥ የንግድ እንቅስቃሴና የኮንትሮባንድ ንግድ በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሳል።
ሰባተኛ፦ እንደ ህወሓት ያሉ አሸባሪ ቡድኖች የሚያደርጉት አፍራሽ እንቅስቃሴ ይቀንሳል።
ለተጨማሪ ማብራሪያ፦